በዓለም ከፍተኛው ተከፋይ የሆኑት መሪ 1 ሚሊዮን ዶላር ደመወዝ ሊጨመርላቸው ነው
የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር እና ሌሎችም ሚኒስትሮች ደመወዝ ሊጨመርላቸው እንደሆነ ተገለጸ።
የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ሎውረንስ ዎንግ በዓለም ከፍተኛው ክፍያ የሚሰጣቸው መሪ ናቸው። ደመወዛቸው በዓመት በ1.1 ሚሊዮን ዶላር እንደሚጨምርም ተገልጿል።
የሚደረግላቸውን የደመወዝ ጭማሪ በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ ለእርዳታ እንደሚሰጡ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት የሚኒስትሮችን ደመወዝ መጨመር ያስፈለገው ችሎታ ያላቸው ባለሥልጣናትን ወደ ኃላፊነት ለመሳብ ነው።
ከዚህ ቀደም የሲንጋፖር መንግሥት ለባለሥልጣናት ከፍተኛ ደመወዝ መስጠት ሙስናን እንደሚያስወግድ አስታውቋል።
የደመወዝ ጭማሪው ትችት ገጥሞታል። በተለይም ከሥራ ደኅንነት እና ከኑሮ ውድነት አንጻር ትችቶች እየተሰሙ ነው።
የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር የደመወዝ ጭማሪ ሳይደረግላቸውም በፊት በዓለም ላይ ከፍተኛ ክፍያ የሚያገኙ የፖለቲካ መሪ ናቸው።
አሁን ላይ ዓመታዊ ደመወዛቸው 2.2 ሚሊዮን የሲንጋፖር ዶላር ሲሆን በተደረገላቸው ጭማሪ ደመወዛቸው 60% በመቶ አድጎ 3.6 ሚሊዮን የሲንጋፖር ዶላር (2.8 ሚሊዮን ዶላር) ደርሷል።
ከሲንጋፖር ቀጥሎ ከፍተኛ ደመወዝ የሚከፈለው ለሆንግ ኮንግ ዋና መሪ ጆን ሊ ነው። ደመወዛቸው 719,000 ዶላር ይደርሳል። በሦስተኛ ደረጃ የስዊትዘርላንድ ፕሬዝዳንት ጋይ ፓርሚሊን ሲሆኑ 606,000 ዶላር ያገኛሉ።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዓመታዊ ደመወዝ 400,000፣ የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር አንዲ ቡርንሀም ደመወዝ ደግሞ 230,000 ዶላር ነው።