የኢራን አብዮታዊ ዘብ፣ ትራምፕ “ውጤታማ የማይሆን” ጦርነት ወይም “መጥፎ ስምምነትን” መምረጥ አለባቸው አለ
የኢራን እስላማዊ አብዮት ዘብ እሁድ ዕለት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት “ውጤታማ ከማይሆን” ጦርነት ወይም “ከመጥፎ ስምምነት” አንዱን መምረጥ አለባቸው አለ።
የደህንነት መስሪያ ቤቱ በኤክስ ገጹ ላይ ባጋራው ልጥፍ ቴህራን ለአሜሪካ ጦር ወደቦቿ ላይ የተጣለው እግድ እንዲያነሳ የጊዜ ገደብ ማስቀመጧን ጠቅሷል።
አክሎም አውሮፓ፣ ቻይና እና ሩሲያ በዋሺንግተን ላይ ቅሬታቸውን እየገለጹ ነው ካለ በኋላ “ይህንን ለመረዳት ያለው አንድ መንገድ ብቻ ነው። ትራምፕ ውጤታማ ከማይሆን ወታደራዊ ዘመቻ ወይም ከእስላማዊ ሪፐብሊክ ጋር መጥፎ ስምምነት ላይ ለመድረስ አንዱን መምረጥ አለባቸው።”
“አሜሪካ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ያላት እድል ጠባብ ነው” ሲልም አክሏል።
አሜሪካ እና እስራኤል የካቲት 21 2018 ዓ.ም ኢራን ላይ ወታደራዊ ዘመቻ ከከፈቱ በኋላ ቴህራን የአጸፋ እርምጃ በመውሰድ የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥን ዘግታለች።
እአአ ከሚያዚያ 13 ጀመሮ አሜሪካ ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረጉ የመርከብ እንቅስቃሴዎችን አግዳለች።
ሚያዚያ 8 የሁለት ሳምንት የተኩስ አቁም በመካከላቸው ተደርሶ የነበረ ቢሆንም በኢዝላማባድ አደራዳሪነት ተጀምሮ የነበረው የሁለቱ አገራት ንግግር ያለውጤት ተጠናቅቋል።
ከዚያ በኋላ ትራምፕ የፖኪስታንን ጥያቄ ተከትሎ የተኩስ አቁሙን ያለምንም የጊዜ ገደብ አራዝመውታል።