ትራምፕ እስራኤል እና ኢራን አሁኑኑ ‘መታኮስ’ ማቆም አለባቸው አሉ
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እስራኤል እና ኢራን አሁኑኑ ’መታኮስ’ ማቆም አለባቸው አሉ።
ፕሬዚዳንቱ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ባጋሩት ጽሑፍ አገራቱ እርስ በእርሳቸው መታኮስ እንዲያቆሙ ጠይቀዋል።
እስራኤል የአጸፋ ምላሽ ከመስጠቷ ቀድም ብሎ ለአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በኢራን ላይ የአጸፋ ምላሽ እንዳይሰጡ አስጠንቅቀው ነበር።
እስራኤል ትናንት በቤይሩት ላይ የፈጸመችውን ድብደባ ተከትሎ ኢራን ወደ ሰሜን እስራኤል ሚሳዔል አስወንጭፋለች።
ይህንን ተከትሎ እስራኤል በመካከለኛው እና ምዕራብ ኢራን በሚገኙ ወታደራዊ ተቋማት ላይ ድብደባ መፈጸሟን አስታውቃለች።
በቴህራን በርካታ ፍንዳታዎች መሰማታቸው ከተገለጸ በኋላ የኢራን አየር መካላከያ በቴህራን ላይ እየበረረ የነበረ ድሮንን መትቶ መጣሉን ሜኸር የዜና ወኪል አስታውቋል።
የእስራኤል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ ለእስራኤል ጥቃት አሜሪካ ኃላፊነት ትወስዳለች ሲሉ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ተናግረዋል።
ባጋይ በመግለጫቸው የእስራኤል አቋም ከአሜሪካ ባለሥልጣናት ጋር እንደሚቃረን በመጥቀስ “በድርድሩ ላይ ጥላውን ያጠላል” ብለዋል።