ከ50 ሚሊዮን በላይ መራጮች
ለሰባተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ ዛሬ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም. መራጮች በየአካባቢያቸው ድምጽ እየሰጡ ነው። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከትግራይ ክልል እና ከአንዳንድ የአማራ ክልል አካባቢዎች ውጪ ምርጫው እንደሚካሄድ አስታውቋል።
ለዚህ ምርጫ 50.5 ሚሊዮን ሰዎች በመራጭነት የተመዘገቡ ሲሆን፣ ይህም አገሪቱ ካላት አዋቂ ሕዝብ ከሁለት ሦስተኛው የሚበልጥ ነው።
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ እንሚያመለክተው ለመራጭነት ከተመዘገቡት ከ50 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን መካከል ሴቶች 46 በመቶ እንዲሁም ወንዶች 54 በመቶ ናቸው።
ዘንድሮ በመራጭነት የተመዘገቡት ዜጎች ቁጥር ከአምስት ዓመት በፊት ከተመዘገቡት በ32 በመቶ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፣ ካለፉት ስድስት ምርጫዎችም የበለጠ ነው።







