እስራኤል ማክሰኞ ዕለት በጋዛ ከተማ በፈጸመችው ጥቃት በዲሱን የሐማስ ወታደራዊ ክንፍ አዛዥ መግደሏን አስታወቀች።
የእስራኤል ጦር በጋዛ ከተማ በተጨናነቀ የገበያ ስፍራ በሚገኝ የመኖሪያ ሕንጻ ላይ በፈጸመው
ከፍተኛ የአየር ድብደባ ቢያንስ ሦስት ፍልስጤማውያን መሞታቸውን የሕክምና ባለሙያዎችና የዓይን እማኞች ተናግረዋል።
ጥቃቱ የኢድ አል-አድሃ በዓል ከመከበሩ በፊት ጎዳናዎች በገበያተኞች ተጨናንቀው ባለበት ወቅት በጋዛ ከተማ መሃል በሚገኘው የአል-ካያሊ ሕንፃ የላይኛውን ሦስት ፎቅ ዒላማ ማድረጉ ተገልጿል።
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ቢሮ ቀደም ሲል የእስራኤል ጦር የሐማስን የጦር ክንፍ አዛዥ መሐመድ ኦዴህን ዒላማ እንዳደረገ አስታውቋል። ይህም የቀድሞው የጦር አዛዥ በተመሳሳይ ጥቃት ከተገደለ ከጥቂት ቀናት በኋላ የተፈጸመ ነው።
ይህ እስራኤል ከሐማስ ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት ካደረገች በኋላ በጋዛ የተፈጸመ የቅርብ ጊዜ ከባድ ጥቃት ነው።
ኦዴህ በጥቃቱ መገደሉን በተመለከተ የእስራኤል መንግሥት ሲያስታውቅ ሐማስ ግን ምንም አስተያየት አልሰጠም።
የነፍስ አድን ሠራተኞች በስፍራው ሲደርሱ በአካባቢው በደረሰው
ከባድ ጉዳት እና በነበረው መጨናነቅ ምክንያት ወደ ላይኛው ፎቅ ለመውጣት ተቸግረዋል።
የዓይን እማኞች ቢያንስ አምስት ሚሳኤሎች ሕንፃውን ከተለያየ አቅጣጫ በተመሳሳይ ጊዜ መምታታቸውን ተናግረዋል።
አንድ ነዋሪ ጥቃቱ ከመፈጸሙ በፊት የሄሊኮፕተር ድምፅ መስማቱን ተናግሯል።
ከቦታው የተገኘ ተንቀሳቃሽ ምስል እንደሚያሳየው አምቡላንሶች እና የሲቪል መከላከያ ሠራተኞች በተመታው ሕንፃ ውስጥ የተረፉ ሰዎች ካሉ ሲፈልጉ የሚያሳይ ሲሆን በአቅራቢያው በርካታ ሰዎች ተሰብስበው ነበር።
የኔታንያሁቢሮ የእስራኤል የመከላከያ ሠራዊት መስከረም 26 2016 ዓ.ም. ሐማስ የፈጸመውን ጥቃት “ካቀነባበሩ ሰዎች መካከል
አንዱን” መሐመድ ኦዴህን ዒላማ እንዳደረገውአስታውቋል።
“ኦዴህ በበርካታ የእስራኤልዜጎችን እና የመከላከያ ሠራዊት አባላት ግድያ፣ ጠለፋ እና መቁሰል ተጠያቂ ነው” ሲል መግለጫውአክሏል።
የቡድኑ ታጣቂ ክንፍ አዛዥ የነበሩት ኢዝ አድ-ዲን አል-ሃዳድ በግንቦት ወር መጀመሪያ ላይ በእስራኤል የአየር ጥቃት ተገድለዋል።
ይህ ጥቃት በአንድ የመኖሪያ ሕንፃ ላይ ያነጣጠረ ሲሆን ቢያንስ ሦስት ሰዎችን ገድሏል ሲሉ የዓይን እማኞች እና የአካባቢው ምንጭ ተናግረዋል።
እስራኤል የተኩስ አቁም ከተደረሰበት እአአ ከጥቅምት 10 ጀምሮ በጋዛ ዙሪያ ጥቃቶችን
ስትፈጽም ቆይታለች።
ሐማስ እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነቱን በመጣስ እና ሲቪሎችን በማጥቃት በተደጋጋሚ ሲከስ ቆይቷል።
የጋዛ የጤና ሚኒስቴር በተኩስ አቁም ስምምነቱ ወቅት በእስራኤል በተሰነዘረው ጥቃት ከ800 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ይፋ አድርጓል።